ሹፌር እና ምርት አሰራጭ ሠራተኛ
Position:
Organization: SNFD Bakery PLC
Not Specified
ድርጅታችን ኤስ ኤን ኤፍ ዲ ኃ/የተ/የግ/ማኀበር ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የስራ ቦታ ላይ ብቁ የሆኑ አመልካቾች አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
የስራ መስፈርቶች
የትምህርት ደረጃ እና ተፈላጊ ችሎታ: ቲቪቲ ደረጃ 4
የሥራ ልምድ: ከ 2-3 ዓመት የሰራ ልምድ
ብዛት : 4
ዋና ዋና ኃላፊነቶች
የስራ ተነሳሽነትና ቅልጥፍና፣ የባለቤትነት ስሜትና የስራ ጥራትን ጠብቆ በታማኝነት፤ በሀቀኝነትና በቅንነት የሾፌር እና የምርት ስርጭት ስራን መስራት፤
ከዋናው ስቶርም ሆነ ከሚኒ ስቶር ለየብራንቹ የሚላኩ ግብአቶችን በኃላፊነት ተረክቦና ፈርሞ ለሚመለከተው ማድረስ
ከስርጭት ሠራተኞች ጋር በጋራ በመሆን ማንኛውንም ምርት ከዳታ ኢንኮደር ሰራተኞች ፈርሞ መረከብና እንደየኦርደሩ ለመሸጫ ሱቆች ሱፐርቫይዘር ወይም ኮኦርድኔተር አስፈርሞ ምርት ማስረከብ
ምርት የሄደባቸውን ፓትራዎች፣ ክሬት፣ሲልቨርና ጐልደን ትሪዎችን ከስርጭት ሰራተኞች ጋር በመሆን በተዘጋጀው መረካከቢያ ፎርም ላይ በአይነትና በቁጥር በመጻፍ ከየብራንቹ ሰብስቦ ለዳታ ኢንኮደር ወይም ለሱፐርቫይዘሮች ማስረከብና በተገቢው ቦታ በጥንቃቄ ማውረድ
.ምርት በሚያሰራጩበት ወቅት እጅን በላስቲክ በመሸፈን ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ምርቱ ሳይበላሽ ማድረስ
የማመልከቻ መመሪያ
ከላይ የተገለፀዉን የሥራ መስፈርት እና የሥራ መደብ የምታሞሉ አመልካቾች ሃያ ሁለት ቅርንጫፍ በሚገኘው ዋናው ቢሮ ወይም ሃይሌ ጋርመንት በሚገኘው ፋብሪካችን በመቅረብ ወይም mulmulhr@gmail.com ማመልከት ትችላላችሁ።
Deadline: Mar 14, 2026, 12:00 AM
Location: Hayahulet
Amount: 4
